Church Faith

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሰቲያን መሰረተ-እምነት

ኢትዮጵያ ከብሉይ ኪዳን ዘመን ጀምሮ አምልኮተ እግዚአብሔር ሲፈፀምባት የኖረች ጥንታዊት ሃገር ነች።በዘመነ-ሐዲስም ክርስትናን በመቀበል ቀደምት ናት። መጽሐፍ ቅዱስና ታሪካዊ ማስረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ኢትዮጵያ በሐዋርያት ዘመን ጥምቀተ ክርስትናን በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ አማካይነት ተቀብላለች (የሐዋ 8÷26-36)። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት (ዶግማ) በመጽሐፍ ቅዱስ እና በሱም ላይ በተመሰረቱት በሶስቱ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች በኒቅያ (325 ዓ. ም.)፤ በቁስጥንጥንያ (481 ዓ.ም.) እና በኤፌሶን (431 ዓ.ም.) በተደነገጉት የሃይማኖት መግለጫዎች ላይ የተገነባ ነው። ከዚህ ቀጥሎ ዋና ዋናዎቹን የቤተክርስቲያናችንን መሠረተ እምነት መግለጫዎች በአጭሩ እናያለን።