ትምህርተ አፁዋማት

ትምህርተ አፁዋማት

በስመ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ አሜን!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አጹዋማትን መሠረት ባደረገ እውቀትን ለማስፋፋት ትምህርት ለምእመናኑ ማዳረስ በጣም አስፈላጊ ነው። የተዋሕዶ ትምህርት በእለተ ቅዳሴ ብቻ በሚሰጡ ቃለ እግዚያብሄር ተዳሶ የሚያልቅ ሳይሆን የእለተ ተእለት መንፈሳዊ ምግባችን ሊሆን ይገባል።

ለዚህም ሲባል በዚህ ክፍል ውስጥ ስለ አጹዋማት በየጊዜው ለምእመናኑ ትምህርት ለማዳረስ የሚሞከር ይሆናል።

ይሁንና በዚህ ዝግጅት ግን እንደ ትምህርቱ ጥልቀትና ምጥቀት ሳይሆን፣ እንደ አዘጋጁ የዕውቀት ውሱንነትና እንደ ተቀባዩ የአእምሮ ስፋት መጠን፣ ግልጽ በሆነ አቀራረብ ይቀርባል።

ፍልሰታ ለማርያም
  • ፍልሰታ ማለት ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ማዛወር የነበሩበትን ሀገር ለቆ ወደሌላ ሀገር መሰደድ መፍለስ ማለት ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሲባልም የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለስንበኋላም በገነት በእፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት የሚነገርነው፡፡
  • እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 64 ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ በሞት ከተለየች በኋላ እንደ አንድ ልጅዋ ሞታመነሣቷንና እርገቷን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት ከነሐሴ 1 እስከ 16 የጾሙት ጾም ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ከሰባቱ አበይትአጽዋማት አንዱ ሆኖ በቀኖና እንዲጾም ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ምእመናን ይጾሙታል፡፡
  • እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከIያቄም ከእናቷ ከሐና “እም ሊባኖስ ትወጽእ መርዓት፡፡ ከሊባኖስ ሙሽራትወጣለች” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡ ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ወረዳ በብጽአትእንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁOት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕትበመሆኗም ማኅደረ እግዚአብሔር ሆናለች፡፡
  • እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከIየሱስ ክርስቶስዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር ጠቅላላ ድምር 64 ዓመትሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
  • ነቢያት አስቀድመው ስለ እመቤታችን እረፍትና ትንሳኤ በምሥጢር ተናግረዋል፡፡ ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር መዝ 136፡8 “አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት” ብሎአል፡፡ ፈጣሪዬ ሆይ ምእመናንን ወደምታሳርፍበት ወደመንግሥተ ሰማያት የመቅደስህን ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ ሲል ነው፡፡ ይህም እመቤታችን እንደ ልጅዋትንሣኤ መነሣቷን የሚያመለክት ነው፡፡ ታቦት ያላትም ማደሪያው ስለሆነች ነው፡፡
  • ጠቢቡ ሰሎሞን “ወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይ እነሆ ክረምት አለፈ ዝናቡም አልፎ ሄደ አበቦች በምድር ላይተገለጡ፡፡ የዜማም ጊዜ ደረሰ የቀረ... ቃል በምድራችን ተሰማ፡፡ በለሱ ጐመራ ወይኖችም አበቡ መዓዛቸውንም ሰጡ፡፡ወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይ” ሲል ስለ እመቤታችን በምሳሌ ተናግሮአል፡፡ መኃ 2፡1አ-13
  • ወዳጁን ውበቱን ተነሺ ነይ እያለ የተጣራው Iየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ተጠሪዋም እመቤታችን ናት፡፡ እነሆ ክረምት አለፈማለት በስደት በአይሁድ የዘወትር ጠላትነት በልጅዋ መከራና ስቅላት ስምOን በቤተ መቅደስ እንደተናገረ ልቧ በሀዘንሠይፍ የተከፈለበት በሀዘን ፍላጻ የተወጋበት የመከራ ክረምት /ወቅት/ አልፎ የክርስቶስ ሕማሙ ፣ ሞቱ፣ ቤዛነቱተፈጽሟል፡፡ ትንሣኤው በምድር ላይ ተገልጧል፣ ተሰብኳል ማለት ነው፡፡ በምድራችን አበባ ታይቷል ማለት የሐዋርያትድምፅ በምድር ሁሉ ደርሷል ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣብሎ ስለ ሐዋርያት የተናገረው በዓለም ያለውን መከራ ስድት ሲገልጽ ነው፡፡ /መዝ 18 ̧4/
  • የዜማም ጊዜ ደረሰ ያለው የመከራን ጊዜ ነው፡፡ ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ በደስታ ይጮሃሉ፣ ይዘምራሉም ተብሏል፡፡መዝ 14፡13 የመከር ጊዜ ደረሰ የተባለው መከር የፍሬ ጊዜ በመሆኑ ክርስትና አፍርቷል ማለት ነው፡፡ በለሱ ጐመራ ማለትደግሞ በጐ ምግባረ ፍሬ ሳያፈሩ የነበሩ ሰዎች በጐ ምግባር መሥራት መጀመራቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በመጨረሻምወይኖች አብበዋል፣ መዓዛቸውንም ሰጥተዋል እንደተባለ በመላው ዓለም አብያተ ክርስቲያናት በሃይማኖት ማበብመዓዛ ምግባራቸውን ማቅረብ ከጀመሩ በኋላ እመቤታችን አረፈች፡፡
  • እመቤታችን ጥር 21 ቀን እረፍት በሆነበት እለት ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለማሳረፍ ወደ ጌቴሰማኒ

መካነ እረፍት ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅንዓት መንፈስ ተነሣሥተው “ቀድሞ ልጅዋን በሦስተኛው ቀን ከሙታንተነሳ፡፡ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ አረገ፡፡ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል፡፡ እያሉ በማስተማርሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጅዋ ተነሣች አረገች እያሉበማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን; ኑ ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት ብለው ተማክረው መጥተውከመካከላቸው ታውፋኒያ የተባለው ጐበዝ አይሁዳዊ ተመርጦ ሄዶ የእመቤታችንን ሥጋ የተሸከሙትን አልጋ ሽንኮርያዘ፡፡ የአልጋውን ሽንኮር በያዘ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሠይፍ ሁለት እጁን ስለ ቆረጣቸው ከአልጋውሽንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ ታውፋንያ በፈጸመው ድርጊት ተጸጽቶ ወደ እመቤታችን ስለተማጸነ በኅቡእ ተአምርየተቆረጡ እጆቹን እንደ ቀድሞ አድርጋ ፈውሳዋለች (ስንክሳር ዘጥር፡፡)

  • የእግዚአብሔር መልአክ የእመቤታችን ሥጋ ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ተድላ ደስታ ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስተነጠቁ፡፡ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፡፡እነርሱም ትወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት፡፡ ያን ጊዜም ከእፅ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችንየማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ ጌታችንም ዘላለማዊ ወደሆነ መንግሥተ ሰማያት መላእክት እና ሰማእታት እየሰገዱላትአሳረጓት፡፡ ንጉሥ ዳዊት “በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋ ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች” እንዳለ፡፡ መዝ 449
  • ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ተመልሶ ከሰማይ ወረደ፡፡ ሐዋርያት ተሰብስበው ስለ እመቤታችን ሥጋፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ እንደሰማ ሥጋዋም በታላቅ ክብር ማረጉን ነገራቸው፡፡ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ፡፡ የነሐሴም ወር በባተ /በገባ/ ቀን ዮሐንስ እንዲህ አላቸው፡፡ የእመቤታችንን ሥጋዋንለማየት ኑ፤ ሁለት ሱባኤ በመጾም እንለምን አለ፡፡ በጾም በጸሎት ሱባኤ ያዙ፤ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ አምጥቶስለሰጣቸው በታላቅ ዝማሬ፣ በውዳሴና በጽኑ ምሕላ ወስደው ቀድሞ በተዘጋጀው መካነ እረፍት በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡
  • የእመቤታችን የቀብር ሥነ ሥርዓት በተፈጸመ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ቶማስ አልነበረምና ከሀገረ ስብከቱ በደመናተጭኖ ወደ Iየሩሳሌም ሲመጣ እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግያገኛታል፡፡ ትንሣኤዋን ሌሎቹ ሐዋርያት አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት ተበሳጭቶ “በመጀመሪያ የልጅሽን ትንሣኤአሁን ደግሞ የአንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ከማዘኑ የተነሣ ከደመናው ተወርውሮ ሊወድቅ ቃጣው፡፡እመቤታችንም ከእርሱ በቀር ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሳኤዋን እንዳላዩ ነግራው አጽናንታው ሄዶም ለሐዋርያት የሆነውንሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው ምልክት ይሆነው ዘንድ ሰበኗን - መግነዟን ሰጥታው አረገች፡፡
  • ሐዋርያው ቶማስም Iየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ እመቤታችንን እኮ ቀበርናት ብለው ነገሩት እርሱም “ሞት በጥር በነሐሴመቃብር እንዴት ይሆናል?” አላቸው፡፡ “አንተ እንጂ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንምን;” ብለውበቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ወደ እመቤታችን መካነ መቃብር ይዘውት ሄደው መቃብሩን ቢከፍቱ ሥጋዋን አጡት፡፡ደነገጡም፡፡ ቶማስም “አታምኑኝም ብዬ እንጂ እመቤታችን ተነሥታ አርጋለች” ብሎ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፡፡ለማረጋገጫ ምልክት እንዲሆን የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡ ሰበኗን - መግነዟን ለበረከት ቆራርጠው ከተከፋፈሉበኋላ ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄደዋል፡፡
  • ሐዋርያትም ትንሣኤሽን ቶማስ አይቶ እኛ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገቡ፡፡በሱባኤው መጨረሻ በነሐሴ አሥራ ስድስት ቀን ጌታችን ጸሎታቸውን ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስጴጥሮስን ንፍቅ ረዳት ቄስ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ ዋና ዲያቆን አድርጐ ቀድሶ ሁሉንም ከአቆረባቸው በኋላየእመቤታችንን እርገቷን ለማየት አብቅቷቸዋል፡፡
  • ቤተክርስቲያናችንም ሥርዓት ሠርታ ከሰባቱ ዓበይት አጽዋማት ተርታ አስገብታ ይህን ታላቅ የበረከትና የምሥጢርመግለጫ ጾም እንድንጾም አድርጋናለች፡፡ ሐዋርያት ያዩትን ድንቅ ምሥጢር የእመቤታችንን ትንሳኤና እርገት ለማየትናከሐዋርያት አበው በረከት ለመሳተፍ ጌታችን “ልጆቼ” ይላቸው ለነበሩ ሐዋርያት አምሳል ሕፃናትና ወጣቶች፣ ሴቶችናወንዶች፣ አረጋውያንም የጻመ ፍልሰታን መድረስ በናፍቆት እየጠበቁ በየዓመቱ በጾም በጸሎት ያሳልፉታል፡፡
  • የእመቤታችን ትንሣኤና እርገት መታሰቢያ - በጾመ ፍልሰታ ወቅት ብዙዎች ከቤታቸው ተለይተው በመቃብር ቤትዘግተው፣ አልጋና ምንጣፍ ትተው፣ በመሬት ላይ ተኝተው ዝግን ጥሬ እፍኝ ውኃ እየቀመሱ በጾምና በጸሎት በመትጋትበታላቅ ተጋድሎ ይሰነብታሉ፡፡ በሰሙነ ፍልሰታ ምእመናን ለእመቤታችን ያላቸውን ጽኑና ጥልቅ ፍቅር የሚያሳዩበትነው፡፡
  • ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር ቆይቶ ሙስና መቃብር ሳያገኘው፣ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብርክፈቱልኝ ሳይል በሥልጣኑ እሑድ በመንፈቀ ሌሊት እንደተነሣ ሁሉ እርሷም በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማኅደረመለኮት ናትና ሙስና መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗትመነሣቷን ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ፤ እንደ ልጅዋ ትንሣኤ” ነው ተብሎ ሲከበርላት ይኖራል፡፡
  • በዚሁ በነሐሴ 16 ቀን የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሰቱ ነው፡፡ ሥጋው ከፋርስ ሀገር ወደ ሀገሩ ወደ ልዳ በክብርየፈለሰበት ነው፡፡ ፍልሰቴን ከፍልሰትሽ አድርጊልኝ፣ ብሎ ለምኗት ስለነበር ፍልሰቱ ከእመቤታችን ፍልሰት ጋር እንዳሰበውሆኖለታል፡፡ ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥእሉን ከሥእሏ አጠገብ ይስላሉ፡፡ በስሙ ለሚማጸኑ የድኅነትወደብ ይሆን ዘንድ፡፡

የእመቤታችን አማላጅነቷ አይለየን አሜን፡፡

ሰሙነ ሕማማት
  • ከትንሳኤ በፊት ያለው ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ቃሉ ሐመ፡ ታመመ ከሚለው ግሥ የወጣ ሲሆን ሳምንቱየጌታችን ሕማሙና ሞቱ ይዘከርበታል፡፡
  •  በተጨማሪም ከአዳም እስከ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን Iየሱስ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት በሲኦል የቆዩበት 5500 የመከራ፡ የፍዳና የኩነኔ ዘመን ስለሚታሰብበት የሕማማት ሳምንት የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ ይህ ሳምንት ቅዱስ፤የመጨረሻ ሳምንትም ተብሎ ይጠራል፡፡
  •  በዚህ ሳምንት Oርቶዶክሳውያን በሙሉ በጠዋት፤ በሦስት፤ በስድስት፤ በዘጠኝና በአሥራ አንድ ሰዓት ወደቤተክርስቲያን በመሄድ የIየሱስ ክርስቶስን ሕማማተ መስቀል ከሚዘክሩ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎች በማንበብናበመጸለይ ሕማሙንና ሞቱን ይዘክራሉ፡፡ በቅዱስ ያሬድ ለዚህ ሳምንት የተዘጋጀውን መዝሙርም በመዘመርአብዝተው ይሰግዳሉ፡፡
  • በዚህ ሳምንት ከጸሎተ ሐሙስ በስተቀር ቅዳሴ አይቀደስም፤ ስብሐተ ነግህ አይደረስም፤ ጸሎተ ፍትሐትናአስተስርዮም አይደረግም፤ ጥምቀተ ክርስትናም አይፈጸምም፡፡ እነዚህ የተዘረዘሩት በሙሉ ስለዚህ ሳምንት በእለተሆሳእና ይፈጸማሉ፡፡
  • ክብረ በዓልም በዚህ እሳምንት ቢውል ከትንሣኤ በኋላ እንዲከበር ይተላለፋል፡፡ - #... በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል እኛ ግን እንደ ተመታ
በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ... ; እንዳለው Iሳይያስ 53 3-12፡፡ የሰሙነ ሕማማት እለታት
  • እሑድ - ሆሳእና - እባክህ አሁን አድን መዝ 117፡25-26 ማለት ሲሆን ጌታችን በአህያይቱና
በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ሕፃናት #ሆሣእና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣእናበአርያም...;ማቴ 21፡9 በማለት የዘመሩበት እለት ነው፡፡
  • ስያሜውንም ያገኘው በእለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡
  • የጸበርት እሁድ (Pአlm Sundአy) ይባላል፡፡ ማቴ 218፡፡
  • በዚህ እለት አምላካችን በድንጋዮችም ተመስግኗል፡፡ ሉቃስ 19፡28-40፤ ዘካ. 9፡9፡፡ ሰኞ
  •  ጌታችን በዚህ እለት ከቅጠል ብቻ በቀር ፍሬ ያልተገኘባትን እፀ በለስ ረግሟል፡፡
ማቴ 21፡12-17፤ ማር 11፡17፤ ሉቃ 19፡45-46፡፡ ይህም እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን የሃይማኖት ፍሬ ምግባር ማጣቱን የሚያስተምረን ነው፡፡ ማክሰኞ
  • በካህናትና በሕዝብ አለቆች #በምን ሥልጣንህ ይኽን ታደርጋለህ; ተብሎ የተጠየቀበት ነው፡፡ ማቴ 21፡23-25፤ ማር11፡27፤ ሉቃ 20፡1-8፡፡ መንግስታችንን ይቃወማል ብለው ለማጋጨት ለቀየሱት ስልት ጌታችንም በአምላክነቱ መልስየማይሰጡበትን ጥያቄ ጠይቆ መልሶላቸዋል፡፡ ማቴ 21፡25፡፡
  • ዛሬም ቢሆን መልካም ሥራን በሠራን ጊዜ ልዩ ልዩ ወገኖች እንቅፋት ሊሆኑ እንደሚችሉ ለቅን አሳባችን ከዓለምየተገላቢጦሽ መልስ እንደሚሰጠን #ዓለም የሚወድደው የገዛ ወገኑን; ዮሐ 15፡19፡፡ እንደሆነ አሳልፈው ሊሰጡንየሚወድዱም ተፈታታኝ ጥያቄ እንደሚያቀርቡልን ያስተማረባት እለት ናት፡፡
የሰሙነ ሕማማት እለታት...
  • ረቡእ -የካህናት አለቆች፤ የሕዝብ ሽማግሌዎችና ጸሐፍት ፈሪሳውያን በጌታችን ላይ
ተማክረዋል ይሙት በቃ ብለውም ፈርደውበታል፤ ጌታችን በስምOን ዘለምጽ ቤት ሳለ አንዲት ከኃጢአትዋ የተጸጸተችሴት ሽቶ ቀብታዋለች፤ ይሁዳ ጌታችንን አሳልፎ ለመስጠት ከፈሪሳውያንና ከካህናት አለቆች 30 ብር ተመዝኖለታል፡፡ ማቴ 26፡3-16፤ ማቴ 26፡24፤ ማር 14፡1-11፤ ሉቃ 22፡1-6፡፡
  • ኀሙስ ኅብስቱንና ወይኑን በባረከ ጊዜ፤ በጌቴሴማኒም ስለጸለየ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡፡ - በዚህ እለት የፋሲካ ዝግጅትተደረገ፤ ጌታችን ሥርዓተ ቁርባንን ሠራ፤ ጌታችን
ጸለየ፤ ይሁዳ አሳልፎ ሰጥቶት ወታደሮች ያዙት፤ ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር አጠበ፤ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱየማጠቃለያ ትምህርት አስተማረ፡፡ ማቴ 26፡11-46፤ ማር 14፡12-52፤ ሉቃ 22፡1-53፤ ዮሐ 18፡1-12፤ ዮሐ 13፡4-17፤ ዮሐ14፡16፤ ዮሐ 16፡16-22፡፡ - የተደረገውንም ለማሰብ ካህናት የምእመናንን እግር ያጥባሉ፤ ከእህልም ጥንት በእስራኤል እንደነበረው በነጻነታችንዋዜማ ለጾም ወቅት ተስማሚ የሆነውን መርጠን ባቄላ እህል ቀላቅለን እንመገባለን፡፡ Iያሱ 5፡11፤ 2ኛ ሳሙ 17፡28-29፡፡
  • ዓርብ ጌታችን ለዓለም ድኅነት በመስቀል ላይ የዋለበት እለት ነው፡፡ - ጌታችን ወደ መቃብር እስኪወርድ ድረስ
  • በሃይማኖት በሊቀ ካህናቱ ፊት ከሰሱት በፖለቲካ ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጥተው በሐሰት ከሰሱት
የሰሙነ ሕማማት እለታት... - ጲላጦስ ወደ ገሊላ ገዥ ወደ ሄሮድስ ልኮት ተጠየቀ
  • -ሄሮድስም ንቆ ወደ ጲላጦስ መልሶት ጲላጦስ መረመረው ጲላጦስ በርባን ተፈትቶ Iየሱስ ግን ተገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ - ፕራይቶሪዮን በሚባለው ግቢ ቀይ ልብስአልብሰው፤ የእሾህ አክሊል
ደፍተው፤ ዘንግ አስይዘው ዘበቱበት
  • መስቀሉን አሸክመው ሊሰቅሉት ወሰዱት
  • በስድስት ሰዓት በጎልጎታ (ቀራንዮ- የራስ ቅል) ቸንክረው ሰቀሉት
  • ልብሱን ለአራት ተከፋፈሉት፤ በእጀ ጠባቡም ላይ እጣ ተጣጣሉ
  • በመስቀል ላይ ሳለ ሰደቡት፤ ተፉበት ሆምጣጤም አጠጡት ጎኑንም
  • በጦር ወጉት -ከስድስት እስከ ዘጠኝ ሰዓትም በመስቀል ቆይቶ በመጨረሻ ነፍሱን
  • ስለሁላችን አሳልፎ ሰጠ ዮሴፍ ዘአርማትያስና ኒቆዲሞስ በአዲስ መቃብር ቀበሩት
  • -ማቴ 26፡37፤ ማቴ 27፡61፤ ማር 14፡53፤ ማር 15፡45፤ ሉቃ 22፡54-56፤ዮሐ 18፡12-42፡፡ አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል
  • -ተኮርOተ ርእስ (ራሱን መመታቱ)፤ አክሊለ ሦክ (የእሾህ አክሊል መድፋቱ)፤ ተአስሮተ ድኅሪት (የኋሊት መታሰሩ)፤ ሰትየሐሞት(ሐሞትና ከርቤ መጠጣቱ)፤ ቅንዋተ መስቀል (ዳናት፤ አዴራ፤
ሳዶር፤አላዶር፤ ሮዳስ)፤ ተቀስፎ ዘባን (ጀርባውን መመታቱ)፤ ርግዘተ ገቦ (ጎኑን መወጋቱ)፤ ተጸፍO መልታህት (ፊቱን መመታቱ)፤ ተአርቆተ ልብስ (ልብሱን መገፈፉ)፤ ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ ተፉበት)፤ ጸዊረ መስቀል (መስቀል መሸከሙ)፤ ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በአይሁድ እግር መረገጡ፤ ወሪደ መቃብር (ወደ መቃብርመውረዱ)፡፡ ቅዳሜ - ቀዳም ስUር የሰሙነ ሕማማት እለታት...
  • ከስድስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት በመስቀል ላይ ሳለ ሰባት ተአምራት ተደርገዋል፡፡ ፀሐይ ጨለመች፤ ጨረቃ ደም ሆነች፤የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ፤ ምድር ተናወጠች፤ ዓለቶች ተሰነጣጠቁ፤ መቃብራት ተከፈቱ፤ ሙታን ተነሡ፡፡ማቴ 27፡45-64፡፡
  • -ጌታችን በመስቀል ሳለ ሰባት የፍቅር ቃላትን ተናግ[ል፡፡ አነርሱም አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅርበላቸው፤ እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ፤ እነኋት እናትህ እነሆ ልጅሽ፤ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ
  • ሰበቅታኒ፤ ተጠማሁ፤ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ፤ ተፈጸመ፡፡ - በዚህም እለት በሰሙነ ሕማማት የተሠራውን ኃጢአት ካህናት የጌታችንን መገረፍ
ለማሰብ በቅጠል እየጠበጠቡ ምእመናንን እንዲሰግዱ ያዛሉ፡፡
  • የድኅነት ሥራውን ፈጽሞ በከርሰ መቃብር አርፏል፡፡ በመጾማችንም የተነሣ ቀዳም ስUር ይባላል፡፡
  • በአዳም ስህተት ምክንያት የገነት ደጅ በጌታችን ቤዛነት ተከፍቷል፤ ጥንተ ርስታችን ተመልሳልናለች፤ አባታችንአዳምም ከእግዚአብሔር ጋር ታረቀልን ስንል #ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ወበትንሣኤሁ አግሃደ; በማለት በኖኅ ዘመን
የተላከች ርግብ ውሃው እንደጎደለ ለማብሰር ቅጠል ይዛ መጥታለችና ቀሳውስትና ዲያቆናት እየዞሩ ቄጠማ ይሰጣሉ፡፡ዘፍጥ 8፡11፡፡
  • ሐዋርያት ጌታችን ከተያዘ ጀምሮ አልበሉምና የሚቻላቸው ሁሉ ያከፍላሉ፡፡ ማቴ 9፡15
ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ጾመ ነቢያት ጾመ አዳም ጾመ ማርያም
በዘመነ ብሉይ ነቢያት እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን፤ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶለአዳም የገባለትን ቃል ይፈጽም ዘንድ ትንቢት በመናገር ለሕዝቡ የምሥራችን ቃል ያበሥሩ ነበር፡፡… ነቢያቱ በጾም በጸሎትተወስነው አምላክ ሰው ሆኖ ዓለምን የሚያድንበትን ዘመነ ሥጋዌ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔርሰው መሆን ተፈጽሟል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስና ሉቃስ፤ ከኅዳር ፲፭ አስከታኅሣሥ ፳፱፤ በዘመነ ዮሐንስ ደግሞ እስከ ታኅሣሥ ፳፰ ጾም ታውጃለች፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢያት እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን፤ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምተወልዶ ለአዳም የገባለትን ቃል ይፈጽም ዘንድ  ትንቢት በመናገር ለሕዝቡ የምሥራችን ቃል ያበሥሩ ነበር፡፡ አምላካችንከድንግል ተወልዶ ከእናቱ ጋር ወደ ግብፅ ምድር እንደሚሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ እንደሚጠመቅ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲልመከራና ስቃይ እንደሚቀበል፣ እንደሚሰቀል፣ እንደሚሞት፣ ከሙታን ተለይቶ እንደሚነሣ፣ እንደሚያርግና ዳግም ለፍርድእንደሚመጣ  በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አስቀድመው ትንቢት ተናግረዋል፡፡ ነቢያቱም የትንቢቱን መፈጸም በተስፋ ይጠብቁ፣ በጾምና በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ይማጸኑ ነበር፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስአስቀድሞ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ‹‹ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣች‰ል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፤ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች›› በማለትም እንደተናገረ ትንቢት ኢሳይያስ ላይ ተጽፎእናገኘዋለን፡፡ (ኢሳ. ፯፥ ፲፬) እንዲሁም ነቢዩ ሚክያስም በቤተ ልሔም እንደሚወለድ እንዲህ በማለት ገልጿል፤ ‹‹አንቺም የኤፍራታ ምድር ቤተልሔምሆይ! አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ነገር ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘለዓለም የሆነ፥በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ከአንቺ ይወጣልኛል፡፡›› ሚክ. ፭፥፪) ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላም ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብፅ ሀገር እንደሚሰደድ እግዚአብሔርአምላክ በነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት አናግሯል፡፡  ‹‹እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጦ እየበረረ ወደ ግብፅ ይመጣል፤የግብፅም የእጆቻቸው ሥራዎች በፊቱ ይዋረዳሉ፤ የግብፃውያንም ልብ በውስጣቸው ይቀልጣል›› እንዲል፡፡ (ኢሳ.፲፱፥፩) ነቢዩ ዳዊትም ‹‹ባሕር አየች፥ ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ‰ላው ተመለሰ፡፡ ተራሮች እንደ ኮርማዎች፥ ኮረብቶችም እንደ በጎችጠቦቶች ዘለሉ፡፡ አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንተም ዮርዳኖስ ወደ ‰ላህ የተመለስህ፟ ምን ሁናችሁ ነው?›› ብሎ እንደተናገረውምሥጢረ ጥምቀቱ ይፈጸም ዘንድ የእግዚአብሔር አምላክ ፍቃዱ ሆነ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም የአብ የባሕርይ ልጅነቱን(የባሕርይ አምላክነቱን) ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር፣ ውኃውን ለመቀደስ፣ የአዳምን ልጆች የእዳ ደብዳቤለመደምሰስና በስህተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ በዮርዳኖስ ወንዝ እንደሚጠመቅ ቀድሞ ተነገረ፡፡ (መዝ. ፻፲፫፥፫) ጌታችንም ከተጠመቀና ለትምህርተ ወንጌል በሚገለጥበት በ፴ ዓመቱ ለብዙዎች ትምህርተ ወንጌልን እንደሚሰብክ እናበጨለማ ውስጥ ላሉት ሕዝብም ሁሉ ብርሃን እንደሚወጣላቸውም የተስፋ ቃል ለሰው ልጅ ሁሉ ተነግሯል፡፡ ይህንንም ነቢዩኢሳይያስ ሲገልጽ፤ ‹‹በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላና በጨለማ ሀገርም ለነበሩ ብርሃን ወጣላቸው›› ብሏል፡፡(ኢሳ. ፱፥፪) ነቢዩም ጌታችን ስለ እኛ መከራ እንደሚቀበል ‹‹እርሱ ግን ስለ ኃጢአታችን ቈሰለ፤ ስለ በደላችንም ታመመ፤ የሰላማችንምተግሣጽ በርሱ ላይ ነበረ፤ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን›› በማለት አስቀድሞ እንደተናገረ በመጽሐፍ ቅዱስ ተመዝግቧል፡፡ ከዚህ ሁሉ መከራና ስቃይ በኋላም ጌታችን ኢየሱስ ሞትንም ድል አድርጎ እንደሚነሣ ‹‹እኔ ተኛሁ፤ አንቀላፋሁም፤እግዚአብሔርም አንሥቶኛልና ተነሣሁ›› በማለት እንዲሁም ተነሥቶ እንደሚዐርግ ‹‹እግዚአብሔር በእልልታ÷ ጌታችንምበመለከት ድምፅ ዐረገ›› በማለት ነቢዩ ዳዊት ትንቢት ተናግbል፡፡ (ኢሳ. ፶፫፥፭፣መዝ.  ፫፥፭፣መዝ. ፵፮፥፭) ይህ ይፈጸም ዘንድ ነቢያቱ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው ሆኖ ዓለምን የሚያድንበትን ዘመነ ሥጋዌ ሲጠባበቁቆይተዋል፡፡ የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔር ሰው መሆን ተፈጽሟል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይህንን ታሳቢበማድረግ በዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስና ሉቃስ፤ ከኅዳር ፲፭ አስከ ታኅሣሥ ፳፱፤  በዘመነ ዮሐንስ ደግሞ እስከ ታኅሣሥ  ፳፰ጾም ታውጃለች፡፡ ነቢያት የጾሙት ይህ ጾም በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት የተለያዩ ስያሜዎች ተሰጥቶታል፤ ሁሉን ነገር በምክንያትየሚያደርገው አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም ድኅነት ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው የገባለት ቃል እንዲፈጸምትንቢት በተነገረው መሠረት ነቢያት ቢጾሙት እና ‹‹የነቢያት ጾም (ጾም ነቢያት)›› ተብሎ ቢጠራም በመሰቀሉ የተቀበለለትመከራ ሁሉ የአዳምን እዳ ይከፍልለት ዘንድ ነውና ‹‹ጾመ አዳምም›› ይባላል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመሆኑም ‹‹የስብከት ጾም(ጾመ ስብከት)››የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመሆኑ ደግሞ ‹‹የልደት ጾም(ጾመ ልደት)›› በመባልም ይታወቃል፡፡ ይህ ጾም ‹‹የፊልጶስ ጾም (ጾመ ፊልጶስ)››ተብሎ ይጠራል፤ የዚህም ምክንያት ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያናአውራጃዋ ሁሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎችአማካይነት በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ስለ ተሰወረባቸው የሐዋርያውን ሥጋይመልስላቸው ዘንድ ሱባኤ ይዘው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው ፈጣሪያቸውን በመማጸናቸው እግዚአብሔር ልመናቸውንተቀብሎ በ፫ኛው ቀን መለሰላቸው፤ ሥጋውንም (አስከሬኑን) በክብር ቀብረውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙበኋላ እስከ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ድረስ ጾመዋል፤ ስለዚህም ጾመ ነቢያት ‹የፊልጶስ ጾም (ጾመፊልጶስ)›› እየተባለ ይጠራል፡፡ በነቢያት ጾም ሐዋርያትም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛም በዚህ ዘመን ከገባንበት ችግርና መከራ አምላካችንእግዚአብሔር ከፈተና እንዲያወጣን በጾም በጸሎት እንማጸን፤ ቸርነትንና ምሕረትንም እንለምን፡፡ ከቅዱሳን ነቢያትናሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ሁላችንም በዚህ የነቢያት ጾም ወቅት በጾም በጸሎትተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡ ምንጭ፡ – ፍትሐ ነገሥት ንባቡና ትርጓሜው፣ አንቀጽ ፲፭ ጾምና ምጽዋት፣ ዲያቆን ቃኘው ወልዴ፤ ገጽ ፵፯ – ፶፡፡
የጽጌ ጾም
(ከመስከረም 26 ( Oct. 6) እስከ ህዳር 5 ( Nov. 15) የሚጾም

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም በተወለደ ጊዜ ንጉሥ ሄሮድስ ሥልጣኔን ይቀማኛልበሚል ቅናት ተነሣሥቶ እርሱን ለማስገደል አሰበ፡፡ ያንጊዜም ጌታችን በተአምራት መዳን ሲቻለው የትዕግሥት፣ የትሕትናአምላክ ነውና በለበሰው ሥጋ በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ በመልአኩ ተራዳኢነት፣ በአረጋዊው ዮሴፍጠባቂነትና በሰሎሜ ድጋፍ ከገሊላ ወደ ግብፅ ተሰዶ ሄሮድስ እስኪሞት ድረስ ቆይቷል፡፡ ሄሮድስም ጌታችንን ያገኘው መስሎትበቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የሚገኙ ሀለት ዓመት ከዚያ በታች የሆኑ አንድ መቶ ዐርባ አራት ሺሕ ሕፃናትን በግፍአስፈጅቷል፡፡

በተአምረ ማርያምና በማኅሌተ ጽጌ ተጽፎ እንደሚገኘው ጌታችን በግብጽ ምድር በስደት ሳለ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትንአድርጓል፡፡ ከእነዚህ መካከልም ውሃ በጠማቸው ጊዜ ውሃ እያፈለቀ ማጠጣቱና ይህንን ውሃ ክፉዎች እንዳይጠጡት መራራማድረጉ፤ ለችግረኞችና ለበሽተኞች ግን ጣፋጭ መጠጥና ፈዋሽ ጠበል ማድረጉ፤ ‹‹የሄሮድስ ጭፍሮች ደርሰው ልጅሽንሊገድሉብሽ ነው›› ብሎ የዮሴፍ ልጅ ዮሳ እመቤታችንን በማስደንገጡ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ድንጋይ ሆኖ እንዲቆይማድረጉ፤ መንገድ ላይ የተራዳቸው ሽፍታ ሰይፉ በተሰበረች ጊዜ እንደ ቀድሞው ደኅና እንድትሆን ማድረጉ፤ እንደዚሁምየግብጽ ጣዖታትን ቀጥቅጦ ማጥፋቱ ተጠቃሾች ናቸው፡፡

የጌታችንና የእመቤታችን የስደት ወቅት በወርኃ ግንቦት ነው፤ ነገር ግን ዘመነ ጽጌ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑእመቤታችንን በአበባ፣ ጌታችንን ደግሞ በፍሬ እየመሰሉ ለማመስገንና ለማወደስ በሚያስችል ምሥጢር ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የስደቱ ጊዜ በዘመነ ጽጌ እንዲዘከር አድርገዋል፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለዘለዓለሙየማይደርቀውን የሕይወት ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስን ያስገኘችልን ንጽሕት የማትጠወልግ አበባ ናትና፡፡ ይህ የእመቤታችንአበባነትና የጌታችን ፍሬነትም እንደ ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና አባ ጽጌ ድንግል ባሉ ሊቃውንት ድርሰቶችበሰፊው ተገልጧል፡፡

የጽጌ ጾም በቤተክርስቲያናችን ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ያሉት አርባ ቀናት ዘመነ ጽጌ (ወርኃ ጽጌ) እንደሚባሉይታወቃል። በነዚህም ቀናት በየቤተ ክርስቲያኑ የሚነበቡ ምንባቦች፣ የሚዘመሩ መዝሙሮች፣ የሚሰበከው ስብከት፣የሚቆመው ማኅሌት፣ በጠቅላላው የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ሁሉ ሰማይ በከዋከብት ምድር በጽጊያት አሸብርቀውየሚታዩ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው። በወርኃ ጽጌ ለሚከናወነው መንፈሳዊ አገልግሎት መነሻው ‹‹መልአኩ ሕፃኑና እናቱንወደ ግብጽ ይዘሃቸው ሽሽ፤ ሕፃኑን ሊገድሉት ይሻሉና›› ሲል ለዮሴፍ በሕልሙ በነገረው መሰረት  ሕፃኑን እናቱን ድንግልማርያምን ይዞ ዮሴፍ ወደ ግብፅ መሰደዱና እመቤታችንና ሕፃኑን ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ ወደአገራቸው ወደ ናዝሬት የመመለሳቸው መታሰቢያ ነው። (ራእይ ፲፪፥፲፮)

በዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡ አባት አባ ጽጌ ብርሃን ‹‹የሮማን ሽቱ የቀናንም አበባ የምትሆኝ ማርያም ሆይ ፥በረሃብ በጾም አበባ የመሰለ የመልክሽ ደም ግባት እስኪ ጠወልግ ድረስ በስደትና በለቅሶ የደረሰብሽን ችግርና ድካምመከራሽንም ሁሉ እንደ እኅትሽ እንደ ሶሎሜ አብሬሽ ብቀበል ምኞቴ ነበር፤ በዚህም ፍጻሜ የሌለውን ደስታሽን እሳተፍነበር።›› ብለዋታል፡፡ እንዲሁም አባ አርከ ሥሉስ በስደቷ የደረሰባትን ኀዘን፣ ልቅሶና ሰቆቃ አስመልክተው በደረሱት ‹‹ሰቆቃወድንግል›› በሚለው ድርሰታቸው እንዲህ አሉ፦ ‹‹ፀሐይን የምትለብሽ የብርሃን ልጅ ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ከሄሮድስዘንድ ልጅሽን ባሸሽ ጊዜ የደረሱብሽን ችግሮች ጨረቃን የሚጫሙ እግሮችሽ በመንገድ ብዛትና በአሸዋ ግለት እንዳጎበጎቡሲሰማ ሰው ይቅርና ድንጋዩም ባለቀሰ ነበር።››

በዚህ ወቅት በሚገኙ ሰንበታትም ሊቃውንቱ ሌሊቱን ሙሉ ስለ እመቤታችን አበባነትና ስለ ጌታችን ፍሬነት የሚያትትትምህርት የያዙትን ማኅሌተ ጽጌና፣ ሰቆቃወ ድንግልን ከቅዱስ ያሬድ ዚቅ ጋር በማስማማት ሲዘምሩ፣ ሲያሸበሽቡ ያድራሉ፡፡ቅዳሴውም በአባ ሕርያቆስ የተደረሰውና ምሥጢረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ሥላሴንና ነገረ ማርያምን የሚተነትነው ቅዳሴማርያም ነው፤ ምንባባቱም ከዚሁ ጋር ተዛማጅነት ያላቸው ናቸው፡፡

የማኅሌተ ጽጌና የጾመ ጽጌ አጀማመር የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ወር በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው በማኅሌት፣በቅዳሴና በዝክር ነው። በወርኃ ጽጌ ባሉት ሳምንታት ከቅዳሜ ማታ እስከ እሑድ ጥዋት አበው ካህናት የሚያቀርቡት ዝማሬከቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ከማኅሌተ ጽጌና ከሰቆቃወ ድንግል የተውጣጣና ሦስት ወገን ያለው ነው። ዝክሩም በአሁኑ ወቅትበከተሞች አካባቢ እየተረሳ ቢመጣም፥ ዘወትር እሑድ የአንድ አካባቢው ሰዎች ማዕከላዊ በሆነ ቦታ ተሰባስበውበእመቤታችን ስም የሚዘክሩት ነው። ዐቅመ ደካሞች ድሆችና መንገደኞች ተጠርተው በእመቤታችን ስም እንዲበሉናእንዲጠጡ ይደረጋል። ይህም ትውፊት እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያ በመጣች ጊዜ ኢትዮጵያውያን እናቶችና አባቶችያደረጉላትን መስተንግዶ ለማሰብ ነው።

የጻድቁ አቡነ ዜና ማርቆስ ዜና ገድል የጽጌን ጾም አስመልክቶ የሚከተለውን ይተርካል፦ ‹‹አባ ጽጌ ብርሃን የተባለው አባት እንደመዝሙረ ዳዊት መቶ ኀምሳ አድርጎ ማኅሌተ ጽጌን ደረሰ። አባ ጽጌ ብርሃን ይህንን በደረሰበት ጊዜ የወረኢሉ ተወላጅና የደብረሐንታው አባ ገብረ ማርያም አማካሪው ነበር። ድርሰቱንም ሲደርስ ቤት እየመታና በአምስት ስንኝ እየከፋፈለ ነው። አባ ጽጌብርሃንና አባ ገብረ ማርያም ከመስከረም  ፳፮ ቀን እስከ ኅዳር ፭ ቀን ማኅሌተ ጽጌን ለመቆምና የጽጌን ጾም ለመጾም በየዓመቱበደብረ ብሥራት እየመጡ ይሰነብቱና ቁስቋምን ውለው ወደየ በአታቸው ይመለሱ ነበር።›› ከአባታችን የገድል ክፍልለመረዳት እንደሚቻለው አባ ጽጌ ብርሃንና አባ ገብረ ማርያም የጽጌን ማኅሌት መቆም ወቅቱንም በፈቃዳቸው መጾምየጀምሩበ ዘመን በዐሥራ አራተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነው።

ከዚያ ወዲህ ግን ጥቂት በጥቂት እያለ አብያተ ክርስቲያናት በወርኃ ጽጌ የጽጌን ማኅሌት መቆም ጀመሩ። ጥቂት መነኩሳትናአንዳንድ ምእመናን በፈቃዳቸው ወቅቱን መጾም ጀመሩ። በዘመናችን በወርኃ ጽጌ የጽጌን ማኅሌት መቆም ስለ ተለመደከማታው በሦስት ሰዓት ይደወላል። ሴት ወንዱ፥ ትንሹም ትልቁም ይሰባሰባል፤ ማኅሌተ ጽጌው እየተዜመ፤ አስፈላጊ የሆነውበጽናጽል በከበሮ እየተወረበና እየተሸበሸበ እስከ ጥዋቱ ፲፪ ሰዓት ድረስ ተቁሞ ይታደራል። የጽጌ ጾም የውዴታ (የፈቃድ) እንጂ የግዴታ አይደለም። የእመቤታችን ስደት በማሰብ ከትሩፋት ወገን የሚጾም ስለሆነ ምእመናን ሁሉ እንዲጾሙትአይገደዱም፤ የሚጾመው የማይጾመውን ለምን አልጾምክም ብሎ ሊፈርድበት ስለ ራሱም እየጾምኩ ነው ብሎ መናገርአይገባውም። የፈቃድ መሆኑንም የሚያሳየው ይኸው ነው፤ የማይጾመውም በልቡ ያመሰግናል፤ ስደቷን እያሰበ ማኅሌቷንእየዘመረ ያሳልፋል።

አምላካችን እግዚአብሔር የጽድቅ ፍሬን ሳናፈራ በሞት እንዳንወሰድ በቸርነቱ ይጠብቀን፤ አሜን፡፡