Church History – (Tinte Tarik)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በጥቂቱ

ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር የምስጢር ሀገር ናት፡፡ አስቀድሞ በነቢዩ ዳዊት «ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች» (መዝ. ፷፯፥፴፩) ተብሎ እንደተነገረላት በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን እንደ ማዕዘን ድንጋይ የሚታዩ ታቦተ ጽዮን እና ግማደ መስቀሉን እጆቿን ዘርግታ ተቀብላለች፡፡ ከሌሎች ክፍለ ዓለማትም ተለይታ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን እምነት አሻራ በጉልህ ይንጸባረቅባታል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከስድስቱ የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክሪስቲያናት ማለትም ከኮፕት (ግብጽ)፣ ህንድ፣ ሶርያ፣ አርመንና ኤርትራ አንዷ ናት። ኢትዮጵያ በመጽሐፍ ቅዱስ ከ፵ ጊዜ በላይ የተነሳች ሲሆን ከክርስትና በፊት የብሉይ ኪዳንን እምነትና ባህል ተቀብላ እግዚአብሔርን ታመልክ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ለአብነት ያህል ጥቂቱን አቅርበን ወደ አዲስ ኪዳን ዘመን እንሸጋገራለን።

ይቀጥላል፣ ይቆየን።
ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር